Category: Article

  • አፋህድ የመንግስት ጂኖሳይዳዊ ወንጀሎች አጋለጠ

    የአፋህድ ወቅታዊ መግለጫ!!!
    /
    በአማራ ላይ በአገዛዙ ወታደሮች የሚፈፀሙ የጾታ ጥቃቶች የጄኖሳይድ ወንጀሎች ስለሆኑ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(UN) አፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ ይገባል!!!
    /
    ህዳር 12፣ 2018 ዓ.ም።
    /
    በአማራ ክልል በሴቶች እና በህጻናት ላይ የአገዛዙ ጦር አባላት በሰፊው የሚፈፅሙት የጾታ ጥቃቶች ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሱ በመሄድ ላይ ናቸው። በታሪክ ጄኖሳይድ በተፈፀመባቸው ሀገራት በውል እንደታየው፣ የፆታ ጥቃት የጄኖሳይደሮች አንደኛው ተመራጭ መሣሪያ ነው። የጥቃት ሰለባዎቹ እድሜ ከ 8 ዓመት አንስቶ እስከ 70 ዎቹ ድረስ መሆኑ፣ ዓላማው ከወሲባዊ አርካታ ይልቅ ህዝብን በሥነ ልቦና ሰብሮ ለተጨማሪ እልቂት እንዲመች ማድረግ መሆኑን በተጨባጭ ያሳያል።

    አማራ ከመንግሥታዊ የጅምላ ጭፍጨፋ ራሱን ለመከላከል እንደ ህዝብ ወደ ትጥቅ ትግል ከገባበት 2015 ዓ.ም አንስቶ፣ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች የተፈፀመባቸው ህፃናት እና ሴቶች በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ናቸው።

    እነዚህ ጥቃቶች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የተፈፀሙት በገጠራማ አካባቢዎች ወይም አንሰተኛ ከተሞች በመሆኑ፣ የህክምና ተቋማት በአቅራቢያ ስለሌሉ አብዛኞቹ ወንጀሎች ተሸፋፍነው ይገኛሉ። ሆኖም፣ አመቺ ሁኔታ ከተፈጠረ ብዙዎቹ ተሸፋፍነው እንደማይቀሩ በጉዳዩ ዙሪያ ጥናት ያደረጉ አካላት አረጋግጠዋል።

    ስለዚህም፣ እንዲህ ዓይነቱ አፀያፊ ወንጀል በጅምላ ሲፈፀም የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በዝምታ ፈፅሞ ሊያልፈው የሚችልበት አግባብ የሌለ በመሆኑ፣ በተባበሩት መንግሥታት (United Nations) የበላይነት ገለልተኛ የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ የሚከተሉት እርምጃዎች እንዲወሰዱ እንጠይቃለን :-

    1—በአማራ ክልል ባለው ጦርነት የተፈፀሙ የጾታ ጥቃቶችን የሚመረምር የባለሙያዎች ቡድን በተባበሩት መንግሥታት አስተባባሪነት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተውጣጥቶ እንዲቋቋም፣

    2— በአማራ ክልል ያሉ ተፋላሚ ወገኖች ለመርማሪ ቡድኑ ያለ ምንም ቅድመና ሁኔታ ቅድሚያ እውቅና እንዲሰጡ፣ በሚቆጣጠሯቸው መሬቶች መርማሪ ቡድኑ በነፃነት እንዲንቀሳቀስ እንዲፈቅዱ፣ ለመርማሪ ቡድኑ የደህንነት ዋስትና እንዲሰጡና ሙሉ ትብብር እንዲያደርጉ፣

    3— መርማሪ ቡድኑ በሚያወጣው የመጨረሻ ሪፖርት መሠረት ተጠያቂዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ፣

    4— በተባበሩት መንግስታት አስተባባሪነት ለተጎጂዎች ደረጃውን የጠበቀ የሕክምና ክትትል ከነፃ መድኃኒት ጋር እንዲሰጥ እና የስነ-ልቦና ድጋፍ እንዲደረግላቸው እንጠይቃለን።

    የጄኖሳይደሮች የተቀነባበረ ሰለባ የሆኑ የአማራ ህፃናት እና ሴቶች ድምፅ ሊሰማ ይገባል። በይበልጥም ፍትህ ሊያገኙ ይገባል። የተባበሩት መንግሥታት በአፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ ይገባዋል። የዘገየ ፍትህ እንደ ተነፈገ ፍትህ ይቆጠራል።

    ክብር እና ሞገስ ጥቃት ለደረሰባቸው የአማራ ህፃናት እና ሴቶች!!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
    /
    ህዳር 12፣ 2018 ዓ.ም።

  • ዘራፊው 103ኛ የአየር ወለድ የአብይ አህመድ ኮማንዶ ድባቅ ተመታ!

    የአፋህድ የህዳር 11፣ 2018 ዓ.ም የአውደ ውጊያ ውሎ—-በሸዋ በፋኖ ጥምር ኃይል በርካታ የጠላት ኃይል ጉዳት ደረሰበት!!
    //
    የህዳር 11፣ 2018 ዓ.ም
    //
    ከአጣዬ (ኤፌሶን) ከተማ ወጣ ብላ በምትገኘው በርግቢ ቀበሌ መሸጎ ለወራት ህዝብን ሲዘርፍና ሲያሰቃይ በቆየው የአገዛዙ የ103ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ላይ ጀግናው የአማራ ፋኖ ጥምር ሠራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።

    ከአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር የተወጣጡ የክፍለ ጦር ሻለቆች፣ በቀጠናው ከሚገኙ የአርበኞች ፋኖ ጦር፣ እንዲሁም፣ የአፄ ዘረ ያዕቆብ ኮር ጀግናው ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር እና ጀግናው የ7ለ70 ክፍለ ጦር በቅንጅት በመሆን ፣ዛሬ፣ ህዳር 11፣ 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11:00 ጀምሮ በርግቢ ዙሪያ በአራት አቅጣጫ ባካሄዱት የተቀናጀ ኦፐሬሽን ከፍተኛ ድል ተቀዳጅተዋል።

    ሰፊ የአውደ ውጊያ ቀጠናን በወሰደው የዛሬው ታጋድሎ፣ በሁለት ወሳኝ ግንባሮች ውጊያ የተደረገ ሲሆን፣ ልዩ ቦታው በጃናሞራ ተራራ፣ በአመጀ ገብርኤል፣ በበርግቢ ውሃ ታንከር እና በቴሌ ታወር አካባቢዎችን የሸፈነ ታላቅ ተጋድሎ የተደረገ ሲሆን፣ በሠራዊታችን የተቀናጀ አንድነት የጠላትን አከርካሪ መስበር ተችሏል።

    በተደረገው የተቀናጀ አውደ ውጊያ አፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆኑት የጀግናው ራንቦ ክፍለጦር ሞገሴ 1ኛ ሻለቃ እና ማንበግር 3ኛ ሻለቃ፣ እንዲሁም፣ የጀግናው 7ለ70 ክፍለ ጦር የናሁሰናይ ፣የሲኖ ሻለቃ ፣እንዲሁም፣ የአስማረ ዳኜ ሻለቃ ታላቅ ተጋድሎ ፈፅመዋል።

    በአማራ ፋኖ ትግል የአንድነት ኃይል በታየበት የአውደ ውጊያ ውሎ፣ በአርበኛ ልመንሕ ዘውዴ የተመራው የጀግናው አፄ ዘረ ያዕቆብ ኮር እና የኮሩ ልዩ ኦፕሬሽናል ክፍል አርበኛ አበባው ዘለቀ የተመራው ሠራዊት፣ ወንድማዊ ፍቅርን ባነገቡ የይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር አሳልፍ ተሻገር ሻለቃ እና የጀግናው 7ለ70 ክፍለ ጦር ደመላሽ ሻለቃ በሌላኛው የአውደ ውጊያ ግንባር ልዩ ቦታው በሳራምባ ቴሌ ታወር፣ በካራ ለጎማ እና በተረተር አካባቢዎች በተደረገው እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ፣ በርካታ የአየር ወለድ ክፍለጦር አባላት ላይ የሰው እና የቁሳዊ ጉዳት ያደረሱበት ሲሆን፣ በቀጠናው የሚገኘው የአገዛዙ ሰራዊት የጀግኖቹን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው ከከሚሴ ከተማ ተጨማሪ ኃይል ቢልክም የጦርነቱን መልክ መቀየር ሳይችል ቀርቷል።

    በከሰያት አመጃ ገብርኤል ተራራው ላይ በሰፈረው የአገዛዙ ሰራዊት ላይ የጀግናው ራንቦ ክፍለ ጦር ሞገሴ 1ኛ ሻለቃ ታላቅ ተጋድሎ በማድረግ በርካታ የጠላት ኃይልን በመደምሰስ፣ የክብር መስዋዕትነት ከፍለው የሻለቆች አንድነት ስኬታማ ድል ተጎናፅፈዋል።

    ጠላት ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለውን የአላላ ጀበል ተራራን ለመያዝ ባደረገው ትንቅንቅ፣ የአገዛዙ ሠራዊት በጀግናው 7ለ70 ክፍለጦር ሲኖ ሻለቃ ተሸንፎ ሲመለስ፣ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የአንድነት ድባብ የታየበት የፋኖ ሠራዊት በአገዛዙ ወታደሮች ላይ የጋራ ድል የተጎናፀፈ ሲሆን፣ ጠላት በሶስት አምቡላንሶች ሙት እና ቁስለኛውን ወደ አጣዬ ከተማ እና ከሚሴ ሆስፒታሎች ወስዷል። የደረሰው ጉዳት ዝርዝር በቀጣይ ይፋ ይሆናል።

    በሌላ ግንባር፣ የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አርበኞች ጦር አርበኛ ታደለ ወርቁ ብርጌድ ቃኝዎች፣ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ ሸዋሮቢት ከተማ 06 እና 03 ቀበሌ፣ መካከል ላይ የሚገኘው ቆቦ ድልድይ አካባቢ በነበረ የአገዛዙ ጦር ላይ፣ዛሬ፣ ህዳር 11፣ 2018 ዓ.ም በሰነዘሩት ድንገተኛ ጥቃት በርካታ የጠላት ኃይል ቁስለኛ ሲሆን፣ ከ5 በላይ የሚሊሻ አባላት ሙት ሆነዋል።

    ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል።

    ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ !!!
    ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
    //
    ህዳር 11፣ 2018 ዓ.ም።

  • አፋህድ በሽዋና በጎንደር አንጸባራቂ ድል ተቀዳጀ!

    አፋሕድ የህዳር 05፣ 2018 ዓ .ም የአውደ ውጊያ ውሎ—በሸዋ እና በጎንደር ደማቅ ድሎች ተመዘገቡ፣ የተሸነፈው የአገዛዙ ጦር ንፁሃን ገበሬዎችን አጠቃ!!!

    — ህዳር 5 ፣ 2018 ዓ.ም።

    በሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በተጉለት አውራጃ፣ ሞጃ እና ወደራ ወረዳ ታምረ ማርያም ፣ ድንሽቅ መገንጠያ ዋሻ መድሀኒያለም አካባቢ ፣አቧራ ፣ግራር አንባ፣ ኮረምቲት፣ደብተሮች፣አባ ሀጉር እና ሳማጉር በተባሉ ስምንት ቦታዎች ከአገዛዙ የ103 እና 104 ክፍለ ጦሮች ህዳር 04፣ 2018 ዓ.ም በከባድ ሁኔታ የተፋለመው ጀግናው የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር የደጅ አዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር፣ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ብሩኬ ደምሴ ሻለቃ፣ በቀጠናው ላይ ያለው የአርበኞች ጦር ሰገነት ብርጌድ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል።

    የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አካል የሆነው መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ጀግናው የደጅ አዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር፣ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ብሩኬ ደምሴ ሻለቃ፣ በቀጠናው ላይ ያለው የአርበኞች ጦር ሰገነት ብርጌድ ከሌሊቱ 7 ሰዓት አንስቶ እስከቀኑ 7 ሰዓት ከጠላት ጋር ባደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ፣ ከደብረ ብርሃን ተነስቶ በመጀመሪያ ወደ ውጊያ የገባውን የአገዛዙን 104ኛ ኮማንዶ አየር ወለድ ወደ ተዘጋጀለት “ሞት ቀጠና” ስቦ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶበታል።

    በዚህ የተደናገጡት የአገዛዙ የጦር መሪዎች፣ ሰላድንጋይ ያለው 103ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ በአጋዥነት ቢልኩለትም፣ ምንም የተለየ ውጤት ሳይገኝ ሁለቱም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ወደመጡበት በሽንፈት ተመልሰዋል።

    የተመታውን የ104ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ለመርዳታ የደረሰው የ103ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለጦር በደረሰበት ጉዳት ተበሳጭቶ ወደኋላ እየተመለሰ ባለበት ግዜ የገበሬዎችን የተሰበሰበ ሰብል እና ቤት በአብሪ ጥይት አቃጥሎ የተለመደውን የጦር ወንጀል ፈፅሟል። በአውደ ውጊያው በጠላት ላይ የደረሰው ጉዳት አየተጣራ ይገኛል።

    ‎የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ልዩ ዘመቻ ኦፕሬሽናል ቡድን ደግሞ፣ ህዳር 04፣ 2018 ዓ.ም በመንዝና ግሼ አውራጃ ሞላሌ ከተማ የሚገኙ ወታደራዊ ዒላማዎችን ለመምታት ወደ ከተማዋ ሰርጎ በመግባት በሰራው አስደማሚ ኦፕሬሽን 6 የአገዛዙ ወታደሮች ከባድ ቁስለኛ ሲሆኑ፣ 2 የተለየ ስልጠና አላቸው የሚባሉ ኮማንዶዎች ደግሞ ሙት መሆናቸው ይህ መግለጫ እስከወጣበት ግዜ ተረጋግጧል።

    በተመሳሳይ፣ የዚሁ የእዙ ልዩ ዘመቻ ኦፕሬሽናል ቡድን ሌላኛው አካል በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ ደብረሲና ከተማ ህዳር 04፣ 2018 ዓ ም ሰርጎ በመግባት የአገዛዙ አየር ወለድ ላይ ባደረሰው ድንገተኛ እና መብረቃዊ ጥቃት 2 የአገዛዙ ተዋጊዎች ተደምስሰው፣ 5ቱ ደግሞ ቁስለኞች ሆነዋል።

    በዚሁ በሸዋ ግንባር፣ የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል በሆነው ጀግናው አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ህዳር 04፣ 2018 ዓ ም ከሌሊቱ 8:00 ላይ ወታደራዊ ዒላማዎች ላይ ብቻ አነጣጥሮ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ፣ በሚዲ እና ሬማ ወረዳ፣ በሬማ ከተማ ዙሪያ በተሰራ ልዩ የከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን፣ አምስት የሚሊሻ አመራሮች ከእነ ትጥቃቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ ስማቸውና ማእረጋቸው ይህን ይመስላል:-

    1ኛ. በሸው አቢቢ ዋና ሻላቃ መሪ
    2ኛ. አቡ ዘለቀው ም/ሻላቃ መሪ
    3ኛ. በለጠ መስፍን ሻምበል መሪ
    4ኛ. እንዳዘነው ግርማ ጋንታ መሪ
    5ኛ. በላይ ከፋለ ጋንታ መሪ

    ምርኮኞቹ የዓለም አቀፍ ህግን በጠበቀ መልኩ ወደሚቆዩበት ስፍራ ተወስደዋል። እነዚህም ሆኑ ሌሎች በድርጅታችን እጅ ያሉ ምርከኞች ከዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ጋር በሚደረግ ግንኙነት ሰብዓዊ መብታቸው ተጠብቆ እጣ ፋንታቸው ይወሰናል።

    የአፋህድ የጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ ህዳር 02፣ 2018 ዓ.ም በጋይንት እና አጎራባች ወረዳዎች ከሀገረ ገነት እስከ ታጥሮ በር ድረስ በነበሩ አውደ ውጊያዎች በተደረጉ ፍልሚያዎች፣ የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር አካል የሆኑት ጀግናው የኮሩ ተወርዋሪ ኃይል፣ ጀግናው የአንበሳው ጋይንት ክፍለ ጦር ፣ጀግናው የተራራው ራስጉና ክፍለ ጦር በጥምር በሰሯቸው ኦፐሬሽኖቸ በአገዛዙ ጦር ላይ መጠነ ሰፊ ጉዳት አድርሶውበታል።

    በደንጓጥ፣ ጎሃ፣ እስላም ቀብር፣ ፈላሺት ፣ከአፋፍ መንደር እስከ ጎሃ ኪዳነ ምህረት በተደረጉ አስደማሚ የጀግንነት ትንቅንቆች ፣ የአገዛዙ ጦር ከብቤዋለኹ ያለውን የወገን ኃይል (ሻምበል አጥናፉ ብርጌድ) ከአደጋ ቀጠና ለማውጣት የኮር፣ የክፍለ ጦር አመራ እና የሠራዊታችን አባላት “እኔ ልቅደም፣ እኔ ልቅደም” በሚል የወንድማማችነት ስሜት የጠላትን ውጥን አምክነው ወገንን ነፃ አውጥተዋል።

    በሌላ በኩል፣ የኃይሌ ዘ ውባንተ ተወርዋሪ ክፍለጦር በስማዳ ወረዳ ሰሞኑን በተደረጉ ውጊያዎች የኳሳ ቀጠና አስደማሚ ድሎችን ተቀናጅቷል። ዝርዝሩን በቀጣይ ቀናት ይፋ እናደርጋለን።

    እውነትም የፋኖ መንፈስ ህያው ነው!!!

    ክብር እና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት !!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
    /
    ህዳር 5፣ 2018 ዓ.ም።

  • በአባት አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ልጅ ሞት አፋህድ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘኑን ገለጸ

    # የሐዘን መግለጫ

    ህዳር 1፣ 2018 ዓ.ም

    ጤና ይስጥልኝ።

    የትግል አባቶች ከሆኑት መካከል አንዱ የሆኑት አርበኛ መሳፍንት ተስፉ፣ ከዚህ በፊት በትግሉ ሂደት ከተሰዋው ልጃቸው አርበኛ ገብሬ መሳፍንት በተጨማሪ፣ ጥቅምት 30፣ 2018 ዓ.ም ደግሞ በቆላ ወገራ፣ አጅሬ ጃኖራ አካባቢ ከአሳቻ ስፍራ ባልተጠበቀ ሁኔታ በተተኮሰ ጥይት ሌላኛው ልጃቸው አርበኛ ጌትነት መሳፍንት መሰዋዕቱን የሰማነው በታላቅ ድንጋጤ እና ሀዘን ነው።

    ምንም እንኳን፣ በሀገራችን “ሰው ሳይሞት አይመሰገንም” እንደሚባለው፣ በህይወት እያለ ልመሰክርለት ዕድሉን ባላገኝም፣ ከሚቀር ረፍዶም ሊነገር ይገባዋልና፣ አርበኛ ጌትነትን እኔ በግሌ አውቀው የነበረ ሲሆንቨ አዲስ አበባ ወደ እኔ መጥቶ የተወሰነ ግዜ አብረን ሰንብተናል።

    በዚህ ግዜ፣ ከዕድሜው በላይ አሳቢነቱን፣ ትዕግሥተኝነቱን፣ ቁጥብነቱን፣ አስተዋይነቱን በቅርቡ ለመታዘብ ችያለኹ።

    አማራ በአራቱም ማዕዘን በማንነቱ በጅምላ የሚደርስበት እልቂት አልበቃ ብሎ፣ አሁንም ከመካከላችን አንዳንዶች እርስ በእርሳችን እንድንገዳደል ማድረጋቸው በስጋ ላይ ብቻ ሳይሆን በታሪክም ላይ የሚፈፀም ወንጀል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።

    ሰው ሆኖ ሰውን መግደል ወንጀል ነው። አማራ በማንነቱ ሳቢያ በመንግሥት በጅምላ እየተጨፈጨፈ ባለበት ሁኔታ ደግሞ፣ አማራ አማራን መግደል የወንጀል ቁንጮ ነው።

    የልጃችን፣ የወንድማችን፣ የትግል አጋራችን አርበኛ ጌትነት መሳፍንትን ነፍስ ቸሩ ፈጣሪ በአፀደ ገነት ያኑርልን፣ አባቱን አርበኛ መሳፍንት ተስፉን እና እናቱን ጨምሮ፣ መላ ቤተሰቡን፣ ዘመድ አዝማዱን እና ጓደኞቹን ያፅናናልን።

    አመሰግናለኹ።

    እስክንድር ነጋ፣
    ከአፋህድ።

  • የአገዛዙ ኮማንዶ በመንዝ ሽንፈትን ተከናነበ፥የወታደሮቹን አድከሬን ጥሎ ሽሽ!

    የአፋህድ የጥቅምት 25፣ 2018 ዓ.ም የአውደ ውጊያ ውሎ— የአገዛዙ ኮማንዶ በመንዝ ሽንፈት ተከናነበ፣ የወታደሮቹን አስከሬን ጥሎ ሸሸ!!!
    /
    ጥቅምት 25፣ 2018 ዓ.ም።
    /
    የአፋሕድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው ጀግናው አፄ ምኒልክ ክፍለጦርን ከሌሊቱ 10:00 ላይ ለመክበብ በማሰብ፣ መነሻውን መሃል ሜዳ ከተማ አድርጎ የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ የ104ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለጦር ፣ በመንዝ ቀያ ወረዳ ልዩ ስሙ “ክምር ድንጋይ” በተባለ አካባቢ ሲደርስ በጀግኖቻችን ከባድ ተኩስ ተከፍቶበት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል።

    የጠላት ኃይል እንደለመደው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የነፍስ ወከፍ እና የቡድን መሣሪያዎችን ተጠቅሞ ብዙ ጥይት ያባከነ ቢሆንም፣ ዒላማቸውን ጠንቅቀው በመለየት በሚተኩሱ ጀግና ተዋጊዎቻችን ሰባት የአገዛዙ ወታደሮች ሙት ሲሆኑ፣ ለግዜው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ደግሞ ከባድ እና ቀላል ቁስለኞች ሆነዋል።

    የአገዛዙ ጦር በሚያሳፍር መልኩ የሞቱ ወታደሮቹን አስከሬን ጥሎ የሸሸ ሲሆን፣ የመንዝ ቀያ ወረዳ ማህበረሰብ አስከሬኖቹን አንስቶ በክብር ቀብሯቸዋል። ቁስለኞቹ ወደ መሃል ሜዳ ሆስፒታል መወሰዳቸው ታውቋል።

    ከአገዛዙ ጦር እየወጡ የአፋህድ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝን የሚቀላቀሉ ወታደሮች ከግዜ ወደግዜ ቁጥራቸው እየጨመረ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ባለፈው ሳምንት በፌድራል ፖሊስ የተለያየ እርከን ኃላፊነት የነበራቸውና፣ አገዛዙ በመከላከያ ሠራዊቱ ያሰለጠናቸው ልዩ ኮማንዶዎች ይገኙበታል። ለወታደሮቹ የክብር አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን፣ በቀጣይነት እንደፍላጎታቸው ወደሚቀጥለው የህይወት ምዕራፋቸው እንዲሸጋገሩ ይደረጋል።

    ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
    /
    ጥቅምት 25፣ 2018 ዓ.ም።

  • በኦሮምያ ያለው የአማራ ጂኖሳይድ የአለምን ትኩረት ይሻሉ ሲል አፋህድ ጥሪ አቀረበ!

    የአፋህድ ጥቅምት 20፣ 2018 ወቅታዊ መግለጫ—በኦሮሚያ ክልል ዳግም የተቀሰቀሱ የጄኖሳይድ ግድያዎች እና ቅስቀሳዎች የዓለምን ትኩረት ይሻሉ!!!
    /
    ጥቅምት 20፣ 2018 ዓ.ም
    /
    በኦሮሚያ ክልል ፣ ምሥራቅ አርሲ ዞን፣ በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም ብቻ የ 2 ዓመት ሕፃን እና የ75 ዓመት አዛውንትን ጨምሮ 25 ንፁሃን በብሄር እና ኃይማኖታዊ ማንነታቸው ሳቢያ በግፍ ተገድለዋል።

    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አባቶች ሰሞኑን ይፋ ባደረጉት ሪፖርት፣ ችግሩ የቆየ ቢሆንም፣ ከዚህ ቀደም ሰላማዊ ተብለው በሚታሰቡ አካባቢዎች እየተስፋፋ ይገኛል። በዚህም መሠረት፣ በጥቅምት ወር ከተፈፀሙት ጥቃቶች መካከል የሚከተሉት ይገኛሉ፦

    1ኛ — በኦሮሚያ ክልል፣ በአርሲ ዞን፣በጉና እና መርቲ ወረዳዎች አዋሳኝ ጥቅምት 14 ለ15 አጥቢያ 17 ሰዎች በብልፅግና ጄኖሳይደር ታጣቂዎች ተገድለዋል።

    2ኛ—በኦሮሚያ ክልል፣ በአርሲ ዞን፣ በሽርካ ወረዳ፡ ጥቅምት 17 ለ18 አጥቢያ ሌሊት 3 ሰዎች በቤታቸው በብሄር እና ኃይማኖታዊ ማንነታቸው ሳቢያ በብልፅግና ጄኖሳይደሮች ታጣቂዎች ተገድለዋል።

    3ኛ— በኦሮሚያ ክልል፣ በአርሲ ዞን፣ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፡ ጥቅምት 18 ለ19 አጥቢያ ሌሊት 5 ሰዎች በብሄር እና ኃይማኖታዊ ማንነታቸው ሳቢያ በብልፅግና ጄኖሳይደር ታጣቂዎች ተገድለዋል።

    በኦሮሚያ ክልል በእንደዚህ ዓይነት ማንነት ተኮር ጥቃቶች ውስጥ በአብዛኛው የመንግሥት መዋቅሮች ተሳትፎ እንዳላቸው ባለፉት 7 ዓመታት ተሞክሮ በተጨባጭ የተረጋገጠ ሐቅ እንደመሆኑ መጠን፣ የኢትዮጰያ መንግስት ገለልተኛ የማጣራት ምርመራ ሊያካሄድ አይችልም።

    ለዚህ እውነታ አንድ ማሳያ የሚሆነው፣ በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ የኖኖ ወረዳ አንድ ኃላፊ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና አመራሮች ባሉበት መድረክ ሰሞኑን ያስተላለፈው የጄኖሳይድ ጥሪ እና ዛቻ ነው።

    የወረዳ ኃላፊው በቅርቡ ወታደራዊ ስልጠና ተሰጥቷቸው ለተመረቁ ወጣቶች ባደረገው ንግግር የሚከተለውን ብሏል :-

    “የአማራ ፅንፈኛ እና መንገደኛ፣ (ወደ ወረዳችን) አርሶ ሊበላ መጣ እንጅ፣ ውስጣችን ቁጭ ብሎ ታገለን አላልነውም። መታገልም አይችልም። አይፈቀድለትም። እንደዚህ ዓይነት መብትም የለውም። እንደዚህ ዓይነት ታሪክም እኛ ጋር የለውም።

    ስለዚህ ለእነሱ ያለንን ተቃውሞ መግለፅ የምንችለው (በቃላት) በመቃወም ብቻ ሳይሆን፣ ታጥቆ የሚወጋንን ገድለን በማሳየት ነው።

    እዚህ ከፊት ለፊቴ ያላችሁት ወጣቶች፣ ይህን ኃይል ባለበት ሳይንቀሳቀስ የምትጨርሱበት፣ በእጃችሁ የያዛችሁትን ዱላ፣ ፈጠሪ ካለ፣ በቅርቡ ወደ ክላሽ ይቀየርላችኋል።

    ክላሽ ግዙ። ጥንድ በሬ ካለህ አንዱን ሽጠህ ግዛ። ነጋዴ ከሆንክ ከንግድህ ቀንሰህ ክላሽ ግዛ። ክላሽ ያለው ይከበራል፣ ያስከብራል።

    እናንተ ግዙ እንጂ እኛ ከጎናችሁ ነን። ፓሊሶችም አሉ፤ ህጋዊ እናደርግላችኋለን።ያደረጉብንን እጥፍ አድርገን እናሳያቸዋለን ” በማለት በአገዛዙ አይዞህ ባይነት ጎረቤት በጎረቤት ላይ እንዲዘምት ግልፅ ቅስቀሳ አድርጓል። (ቪዲዮውን አያይዘናል።)

    ስለዚህም፣ በቀጠናው ያሉ የሚሊዮኖች ህይወት አደጋ ላይ የወደቀ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአፋጣኝ ጉዳዩን በገለልተኝነት አጣርቶ እንዲደርስላቸው እናሳስባለን። በመንግስት ኃይሎች የሚፈፀሙ ማንነት ተኮር ግድያዎች የአንድ ሀገር የውስጥ ጉዳይ ሳይሆኑ፣ የመላው ዓለም ጉዳይ ናቸው።

    በተጨማሪም፣ ይህን እኩይ ድርጊት ኦሮሞን ጨምሮ መላ ኢትዮጰያዊያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እንዲያወግዙት እና እንዲታገሉት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

    ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
    /
    ጥቅምት 20፣ 2018 ዓ.ም።