Category: Article

  • የአገዛዙ ጦር ሙትና ቁስለኛ ሆነ

    አፋህድ ጥቅምት 06፣ 2018 ዓ.ም የአውደ ውጊያ ውሎ— የአገዛዙ ጦር ሙት እና ቁስለኛ ሆነ፣ መኮይ ከተማ ተከባለች!!!
    ‎/
    ጥቅምት 06፣ 2018 ዓ.ም።
    /
    የአፋህድ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ 206ኛ ኮር፣ ከትላንት ሌሊት አንስቶ እስከ ዛሬ፣ ፣ጥቅምት 6፣ 2018 ዓ.ም ድረስ በጨጨሆ እና ጋንጋ ላይ ከባድ ውጊያዎችን ሲያደርግ ውሏል።

    የጠላት ጦር ከታች ጋይት እና ጎብጎብ ብዛት ያለው ኃይል አሰባስቦ ወደ ውጊያ ቢገባም፣ የነበልባሎቻችንን ምላሽ መቋቋም ተስኖት፣ ከሙት እና ጉዳት የተረፉትን የመከላከያ፣የአድማ ብተና፣ የሚሊሻ እና የፖሊስ አባላቱን ይዞ ምሽጉ ወዳደረጋቸው ታች ጋይንት እና አርብ ገበያ ከተሞች በሽንፈት ተመልሷል።

    በአውደ ውጊያዎቹ 25 ሙት እና ከ40 በላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ቁስለኞች እንደነበሩ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ግዜ ታውቋል። አጠቃላይ መረጃው በቀጣይ ቀናት ይፋ ይሆናል።

    በሌላ አውደ ውጊያ፣ ወደ አጋጥ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል የጀግናው ገብርዬ ክፍለ ጦር አካል የሆኑ ሁለት ብርጌዶችን ለማፈን ቢሞክርም፣ ከጠዋቱት 12:00 ሰዓት ጀምሮ በነበረው ውጊያ በጀግናው ሠራዊታችን ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበታል።

    በዚህ አውደ ውጊያ ጠላት በደረሰበት ጉዳት ተበሳጭቶ በሲቪሎች ላይ ባደረሰው የበቀል እርምጃ በቀበሌ 12፣ ልዩ ስሙ “ወንቢ” በሚባል ቦታ ከእርሻ ማሳቸው በስራ ላይ የነበሩ አርሶ አደሮችን በግፍ ረሽኗል። ወንጀሉን የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲያጣሩ እንጠይቃለን።

    የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አካል የሆነው ጀግናው አስቴጎማ ተራራ ክፍለ ጦር፣ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ ይፋት አውራጃ፣ በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ የአገዛዙ ጦር እስካለበት ድረስ በሰርጎ ገብ ኦፕሬሽን ሰርገው በመግባት ከጠላት ወታደሮች ጋር በጨበጣ ውጊያ ተናንቀው ከፍተኛ ጉዳት አድርሰውበታል።

    ከጥቅምት 2 እስከ 6፣ 2018 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ቀናት ተፋፍሞ በሚገኘው አውደ ውጊያ፣ በይፋት አውራጃ፣ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ የምትገኘው መኮይ ከተማ በጀግናው ሠራዊታችን ከበባ ውስጥ ገብታ የአገዛዙ ጦር በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል።

    ጀግናው አስቴጎማ ተራራ ክፍለ ጦር በመኮይ ከተማ ዙሪያ ባሉት በአርባ አራቱ ቀበሌ፣ በወበሻ ቀበሌ፣ በመቅደሳ ቀበሌ፣ በ04 ቀበሌ፣ በ05 ቀበሌ ገዢ መሬቶችን በመያዝ የጠላት ጦር ገና ከምሽጉ ብቅ ሲል ከባድ የሰብዓዊ እና ቁሳዊ ዋጋ እንዲከፍል እያደረጉት ይገኛል።

    ውጊያው ለቀጣይ ቀጠናት የሚቀጥል ሲሆን፣ በማጠቃለያው በሚኖረን መግለጫ በጠላት ላይ የደረሰውን ጉዳት በዝርዝር እናቀርባለን።በዚህ መግለጫ፣ ለአብነት እንዲሆን አገዛዙን ከድቶ ፋኖን የተቀላቀለ ኦሮምኛ ተናጋሪ የኮማንዶ አባል ምስልን ከእነ ዘመናዊ ስናይፐሩ አቅርበናል። ስርዓቱ የሚተማመነው በእንደዚህ ዓይነቱ ወታደር ቢሆንም፣ አሁን እየከዳው ይገኛል።

    በሌላ አውደ ውጊያ፣ ዛሬ፣ ጥቅምት 06 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11 ሰዓት 30 በአገዛዙ የ 112ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር በመንዝ ቀያ ወረዳ፣ ከዘመሮ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የአመጃ ቀበሌ፣ ልዩ ስሙ “ጫት ውሃ” በተባለ ቦታ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው ጀግናው ምኒልክ ክፍለ ጦር በፈፀመው የደፈጣ ጥቃት ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል።

    መነሻውን ከዘመሮ ከተማ አድርጎ ወደ ዘረት በመንቀሳቀስ ላይ የነበረው ጠላት በጀግኖቻችን በተፈፀመበት ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት በመሆኑ፣ ተጨማሪ ኃይል ከመሃል ሜዳ እንዲላክሎት ጠይቆ፣ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ግዜ ድረስ ውጊያው እንደቀጠለ ይገኛል። ውጤቱ በቀጣይ ቀናት ይፋ ይሆናል።

    ትግሉ ተፋፍሞ ይቀጥላል።

    ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት !!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
    /
    ጥቅምት 06፣ 2018 ዓ.ም

  • ይድረስ ለአማራ ዲያስፖራ

    አርባ ቀን ወይስ 40 አመት?
    ከሞገድ እጅጉ
    (አማራ እንደ እስራኤላውያን)
    እስራኤላውያን 432 አመት በግብፅ ምድር በባርነት ተገዙ። እግዚአብሄር በመጨርሻው ወደ እነርሱ ሄደ። ከፈርኦኑም እጅ ነፃ ወጡ።
    ጉዞ ወደ ከነአን ተጀመረ። የአርባ ቀን ጉዞ ነበር። 40 ቀናት ብቻ! ነገር ግን የተስፋውዋን ምድር ለማየት 40 አመታት ፈጀ።
    ምን ተፈጠረ?
    “back to the wilderness” እንደገና ወደምድረበዳ ተመለሱ። የተሳካ ጉዞ ሊሆን ሲችል ይህ ጉዞ እንዴት ሊበላሽ ቻለ? ብለን ስንጠይቅ መልሱ ተስፋ፣ እምነት እና ፍቅር ማጣት ይሆናል ። ተስፋ የቆርጠ ሕዝብ በበረሀ ይቀራል። እምነትም የሌለው ሕዝብ በበረሀ ይቀራል። ፍቅርም የሌለው ሕዝብ በበረሀ ይቀራል።
    እኛ አማሮች እንደእስራኤላውያን ባርነት አላጋጠመንም። የፈርኦንም ሆነ የቄሳር ቀንበር አልተጫነብንም። ነገር ግን በራሳችን ባርነት ውስጥ ነው ያለነው። ራሳችን በሰራነው ባርነት ውስጥ ወድቀናል።
    እስራኤላይውያን አምነው ወጡ። ነገር ግን በጉዞው ላይ ፈጣሪያቸውን ሊኖሩት አልቻሉም። ወደኋላ እያዩ ወደ ምስር ምድር. . .
    እኛ የአማራ ተወላጆች የገጠመን አሁናዊ ሁኔታችን ይኸው ነው። በራሳችን የኔ እበልጣለሁ ባርነት ወድቀናል። ከፍ ሲል የኔ “ክልል” ዝቅ ሲል የኔ አውራጃ በሚል አስተሳሰብ ተጠልፈናል።
    ወያኔ አማራውን ጠባብ እና ጽንፈኛ ብሄርተኛ ለማድረግ 27 አመት ዳከረች። አልተሳካላትም። አማራው ላይ ያልተፈጸመ በደል የለም። ጭቆና፣ መድሎ ፣ መሳደድ መፈናቀል ፣ ተለይቶ መጠቃት አማራ ቢገጥመውም አንገቱን ቀና አድርጎ ትከሻውን ሰብቆ ከፍ ሲል ኢትዮጵያዊ ዝቅ ሲል አማራዊ አስተሳሰቡን እሴቱን መጠበቅ ችሎ ነበር።

    እርግጥ ነው የተማረ መሪ ነበረን። ያወቀ መሪ ነበረን። መሪ ስንል ደግሞ የተመራመረ መሪ (caltvated in the intelectual level) ማለታችን ነው። እንደ ፕሮፌሰ አስራት ወልደየስ (አብዬ አስራት) ማለታችን ነው።
    አማራ መንግስታዊ ጥቃት የደረሰበት ከደርግ ጊዜ ጀምሮ ነው። ደርግ በአዋጅ አማራ እንዲገደል አድርጓል። በአዋጅ ሀብት ንብረቱን ዘርፏል። እንዲደኽይ አድርጓል። በስተመጨረሻም ደርግ ለወያኔ አቀብሏታል። ደርግ ፊውዳል በሚል የሽፋን ስም ሲፈፅመው የቆየውን ወያኔ ትህምትተኛ ብላ ቀጠለች።
    አማራ፦ በወያኔ ጊዜም ሀብት ንብርቱን ተነጥቆ እንዲኮሰምን ተደርጓም። መንግስታዊ መዋቅራዊ አድሎና መገለል (systemic political alienation )ተፈጽሞበታል። ለ27 አመት ግን አንገቱን ቀና አድርጎ ትከሻውን ሰብቆ ወያኔን ተታግሎ አሸንፎታል ብሎ 27 አመት ተታግሎ ያመጣው አብዮት ታዲያ በራሱ በአማራው የፖለቲካ ብስለት ማጣት በኦሮሞ ብልጽግና ማደናገርና ማሳመን (confused & convince) በሚባል ከኦሮሙማ ጋር ብቻ በሚገኝ ስሁት ፖለቲካዊ እሳቤ ተታልሎ ከፖለቲካ ጭዋታው ውጭ ተደርጎ እለት በእለት እየታረደ ይገኛል። ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል አይደል ተረቱ
    በሌላ መልኩ መሪ ያጣ ህዝብም ሆኗል።
    ፕሮፌሰር አስራትን ሸኝተን ዶ/ ር በለጠ ሞላን አየን። የእሳት ልጅ አመድ ማለት ይህ ነው።
    አዎ የወያኔን መዋቅራዊ ጥቃት አማራው ቀለበስኩ ሲል አሁንም እዚያው የለመደው መከራ ውስጥ ነው። ይባስ ብሎ በነብሰ በላው ዘራፊውና ስግብግቡ የአብይ አህመድ ድራጎናዊ አገዛዝ እጅ ወድቆ የአፓርታይድ መዋቅር ተዘረጋበት።
    በ2013 ሀምሌ ወር የአማራ ህዝብ የአብይን መንግስት በቃኝ አለ። ፋነነ…ፋኖ ተሰማራ። በ17 ወራት ውስጥ ምንም የውጭ ድጋፍ ሳያገኝ የአማራ መስተዳድር ከተሞችን ተቆጣጠረ። ገጠሩን በጠቅላላ ተቆጣጠረ።
    እስራኤሎች 40 ቀን ሆናቸው። ወደ ከነአን ተቃረቡ። ሆኖመ‍እ አምላካቸው ወደ ነበሩበት የሲና በረሀ፣ የቀይ ባህር መዳረሻ ወደነበረው ሀህሮዝ ካምፕ ተመለሱ አላቸው። ከነአንን አላወርሳችሁም አላቸው። ወደ ተስፋዋ ምድር አትገቡም አላቸው። እስራኤሎች ወደ በረሀው ተመለሱ። በዚያም 40 አመት ቆዩ። (ዘ-ጸአት ምዕራፍ 13-14 ይመልከቱ)
    ይህን ጉዞ ሳስብ አሁን ካለው የአማራ ትግል ጋር ይመሳሰልብኛል። ከነአንን ልንወስድ ሲገባ እርስበርስ የአማራ ልጆች ስንባላ የያዘነውን ድል ልንነጠቅ ነው። እኛም ወደ ምድረበዳ እየተንከራተትን ነው። በዚሁ ከቀጠልን ደግሞ አሁን ያለው ትውልድ እንደስራኤሎች ይጠፋል የሚል ስጋት አለኝ። ምናልባትም የተስፋዋን ምድር የምንናፍቃትን ኢትዮጵያን ለማየት 40 አመት ወይም ከዚያ በላይ ሊፈጅብን ይችላል።
    እስራኤሎችን ፈጣሪያቸው ወደ ምድረ በዳው ለምን ተመለሱ አላቸው?
    ምክንያቱም ለፈጣሪያቸው አልታዘዙም። ከፈጣሪያቸው መና ይልቅ የግብጽን ጮማ ናፈቁ፣ አንድነት አጡ ፣ ፍቅር አጡ ተስፋ ቆረጡ። በመጨረሻም በረሀ በላቸው። ከመጀመሪያው ትውልድ ከ2 ሰው በስተቀር ከነንን ያያት የለም።
    የአማራም ትግል
    ዘ ጸአትን ይደግም ይሆን?
    የአማራ ትግል ከድጡ ወደ ማጡ እየሄደ ያለው አርቆ አስተዋይ በማጣቱ ነው፡፡ ጠላትና ወዳጁን መለየት የሚችልና በፖለቲካዊ ብልጠት መጓዝ የሚችል ደጋፊ በማጣቱ ነው፡፡ አብዛኛው ራሱን በራሱ የሚበላ እየሆነ ነው፡፡ ከገዳዩ ጠላት በላይ የራሱን ሰው ጠላት አድርጎ የሚታገል በመሆኑ ነው፡፡
    የአማራ ህዝብ ማን ነበርን ማን ነን?

    የአማራን ህዝብ 5 ሺ ዓመት የዘለቀ ታሪክ ለመጻፍ አቅሙ፣ በቂ እውቀቱም ኖሮኝ አይደለም። በወፍ በረር ግን ቁጭቴን ታሪክን አጣቅሼ ልግለጽ ብዬ ነው።
    ጀግናው የአማራ ሕዝብ ከዓለም ቀድሞ ሥልጣኔን ያስጀመረ፣ ለነገሮች ሁሉ ችግር ፈቺ መፍትሔ ማፍለቅ የሚችል፣ የመገልገያ ዕቃዎችን በራሱ ፈጠራ ገጣጥሞ የሚጠቀም፣ ትምህርት የሥልጣኔ መነሻ ነው የሚባለውን ፊደል ቀርጾ የጽሕፈት ሥልጣኔ የጀመረ ሕዝብ ነው፡፡
    የአማራ ሕዝብ ስነ ልቦናዊ ፍልስፍና ያለው፣ ዛሬን ሳይሆን ነገን አርቆ የሚያስተውል፣ ጨዋነትንና ጀግንነትን፣ አብሮነትንና ለጋስነትን የተቸረ ሕዝብ ነው፡፡
    የአማራ ሕዝብ በእያንዳንዱ ስነ ልቦናዊ ጉዳይ ላይ ያለውን እምቅ ፍልስፍና ለማወቅ የሕዝቡን ስነ ቃል ማየት በቂ ምስክር ነው፡፡ ሌላ ጊዜ በዝርዝር እንመለስበታለን፡፡
    ይህ ሕዝብ ለምን አመድ ወለደ?
    ‹‹ዘመናዊ›› የሚባለውን ትምህርት የተማርነው የአሁኖቹ የአማራ ልጆች ምን እንደነካን አይታወቅም! ከአማራ ሕዝብ ስነ ልቦና የራቅን ሆነናል፤ እጅግ ኋላ ቀርና ነገር ማሰብ የማንችል ሆነናል።
    በጣም ግልጽ የሆኑ ነገሮችን ማስረዳት ይሰለቻል፤ ይደክማል! ‹‹አማራ ከጎጥ አስተሳሰብ ወጥቶ አንድ ይሁን! ይደራጅ!›› ብዬ ለመጻፍ ሳስብ በአማራ ጠላቶች መሳቂያ የሚያደርገኝ ይመስለኛል! ትክክልም ናቸው! ጤነኛ በመሆን ብቻ ልናውቀው የሚገባውን ግልጽ ነገር መናገር አድካሚ ነው፡፡
    አማራ ግን ለምን አመድ ወለደ?
    የአማራ ነገር ‹‹እሳት አመድ ወለደ!›› የሚለውን አባባል ያስታውሰኛል፡፡ በዲፕሎማሲ፣ በጦር አርበኝነት፣ በኪነ ጥበብ ከያኒነት…. በአጠቃላይ በሁሉም ዘርፎች ኢትዮጵያን ያቀና ሕዝብ እንዴት እዚህ ላይ ወደቀ? እነዚያ ነበልባል የነበሩ ሰዎች እንዴት አመድ ወለዱ? እነ ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስን ያፈራ ምድር እንዴት እነ በለጠ ሞላን ሊቀበል ቻለ?
    ደፈር ብለን እንናገር ከተባለ አሁን አማራን እወክላለሁ የሚለው ኃይል ፈሪ እና ሆዳም ነው፡፡ ይሄ በግልጽ ሊነገረው ይገባል፡፡ ሥልጣን የሚያጓጓው ሆዳም ሆኗል፡፡
    ለምሳሌ፡-ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚሰማው ነገር ጎጠኝነት ነው፡፡ ከዚህ በላይ አስቂኝ አላዋቂነት የለም፡፡ የእሱ ጎጥ ሰላም የሚሆነው አጠቃላይ አማራ ክብር ሲያገኝ መሆኑን አያውቅም፡፡ ጠላቶቹ የመጡበት ጎጃም፣ ጎንደር፣ ሸዋ ወይም ወሎ ብለው ሳይሆን አማራ ብለው ነው፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ ቤቱን ያፈረሱበት ጎጃሜ ወይም ጎንደሬ፣ ሸዋዬ ወይም ወሎዬ ብለው አይደለም፤ አማራ ብለው ነው፡፡ ሰው እንዴት ይሄን መረዳት ይቸግረዋል?
    አብይ አህመድ ጎጃም እና ጎንደርን ለመከፋፈል ‹‹ጎንደርን ሳለማ ጎጃሞች ‹ምን ዋጋ አለው ጎንደር ሆነ! አሉኝ›› ብሏል፡፡ በእሱ ቤት ጎጃም እና ጎንደርን መከፋፈሉ ነው፡፡ ሰው እንዴት በዚህ ሰውዬ ይሸወዳል?
    አብይ አህመድ የትግራዩን ጦርነት ሊያስጀምር ሲል የአማራ ወዳጅ መስሎ ነበር፡፡ ሥልጣን በያዘ ገና በ3ኛ ወሩ ‹‹ትግሬ አማራን ለማጥፋት መሥራት የጀመረው አሁን አይደለም›› አለ፡፡ እዚህ ላይ ልብ መባል የነበረበት ነገር ትግሬ አማራን አጥቅቷል ወይስ አላጠቃም የሚለው አይደለም፡፡ ከአብይ አህመድ ንግግር ሊገርመን ይገባ የነበረው እንደዚህ ማለት ለምን ፈለገ የሚለውን ነው፡፡ በወያኔ ጊዜ አማራ ላይ ግፍ ይፈጸም ነበር የሚለውን የአማራ ምሁራን ቅሬታ ያስታውሳል፡፡ ስለዚህ በዚያን ወቅት ያንን ሲናገር አርቆ ማሰብ በማይችሉ አማሮች እንደሚወደድ ስለገባው ነው፡፡ አርቆ ማሰብ ማለት ትግሬ በአማራ ላይ ግፍ አልፈጸመም ማለት አይደለም፤ ዳሩ ግን ይህን ሊነግረኝ የሚገበው እንደ አብይ አህመድ አይነት መሃይም እና ጨካኝ አውሬ አይደለም፡፡
    አብይ አህመድ ያኔ የአማራ ተቆርቋሪ መስሎ በኋላ ምን አደረገ? አፈ ሙዙን ወደ አማራ አዞሮ! አማራን መተታም እና ኋላቀር እያለ መሳደብ ጀመረ፡፡ ከዚህ ምን እንረዳለን?
    አንዱን የመውቀስ ሌላውን የማሞገስ አላማ አልያዝኹም። ነገር ግን ይህ የተራዘመ በአማራ መስተዳድር ላይ የታወጀ ጦርነት በይፋ 3 ኛ አመቱን ይዟል። ቀደም ብሎ ለ2 አመት ይፋዊ ያልሆ ጦርነት ነበር። በጥቅሉ 5 አመት ሆነው።
    ባለፉት አምስት አመታት በአገር ውስጥ የተፈናቀሉ አማሮች ቁጥር 4 ሚሊዮን እንደሚጠጋ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት (ኦቻ) በአውሮፓውያኑ መስከረም 10 ቀን 2024ዓ ባወጣው ሪፖርት አሳውቋል። (አዲሱን ሪፖርት በዲሴምበር ይወጣል የከፋ እንጂ የተሻለ አዮንም) ።2024 ሪፖርቱን ራሳቸው የአማራ መስተዳድር ባለስልጣናት ጀብዱ የሰሩ ያክል በደስታ ተቀብለውታል።
    በክልሉ ላይ ለደረስ ሁለንተናዊጥፋት እና ኪሳራ የሚደስት አለ ብሎ ማመን እንደሰው ይከብዳል።የበአዴን /ብልጽግናዎች ግን ችግሩ ከጭንቅላታቸው ላይ ይሁን ጆሮአቸው ላይ አስደስቷቸዋል።የኦቻ ሪፖርት ሲቀጥል ፦ እንዲህ ይነበባል።
    በመስተዳድሩ በዘጠኝ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 43 ወረዳዎች እና 429 ቀበሌዎች ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በድርቅ ተጎምድተዋል። የፌዴራሉ አገዛዝ 1 ሚሊዮን ብቻ ነው ያመነው። 3 ሚሊዮን 556 ሺ 239 ተፈናቃዮች አሉ።፣ በድምሩ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች የዕለት ምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የመንግሥታቱ ድርጅት ገልጿል።
    5552 ትምህርት ቤቶች የ1ኛ ደረጃና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከጥቅም ውጭ ተደርገዋል። 5772 ጤና ጣቢያዎች ክሊኒኮች ፣ ጤና ኬላዎች ሆን ተብሎ በአገዛዙ ወታደሮች ወድመዋል።
    ቀድሞ በ (USID undersevilance) የነበሩ የተለያየ በሽታ ተከታታዮች ድርጅቱም በመዘጋቱ እንዲሁም ጦርቱ ውድመት ባስከተለው የአገልግሎት እጦት እያለቁ ነው።
    የአብይ አይመድ ወታደር ልጃገዶችን እየደፈረ ነው። ኤች አይ ቪ ኤድስ በማስፋፋት ላይ ነው። ወሲብን እንደ ጦር መሳሪያ በመጠቀምም ከበሽታ ያመለጡት እንዲወልዱ እየተደረጉ ነው።
    ቀድሞ 11.6 ሚሊዮን ተማሪዎች በአመት ያስተምር የነበረው የአማራ ህዝብ አሁን 2.1 ብቻ ነው እያስተማረ ያለው። ለዚያው ይህ ቁጥር ውሸትን ግብሩ በአደረገው አገዛዝ ይፋ የተደረገ ነውና ተአማኒነቱ አጠያያቂ ነው። ይህ የቀጠለው ላለፉት አምስት አመታት ነው። ምን ያህል የትውልድ ክፍተት ሊፈጥር ሊፈጠር እንደሚች ይታሰብ። የ51 አመት በፊት ደርግ ስድሳ ምሁራንን ረሸነ። እነኝህ ምሁር ባለስልጣናት አብዛኞቹ ከልጅነታቸው ዘመን ጀምሮ ለሀገር መሪነት በመታጨታቸው የአብነት ከቅኔ እስከ ድጓ ያጠኑ፣ ቢያንስ ዳዊት የደገሙ ነበሩ። በአስኳላ ትምህርት በሕግ፣ በምጣኔ ኃብት፣ በፖለቲካዊ ሳይንስና የሕዝብ አስተዳድር፣ በካዴትነት ተደራራቢ ዘርፎችን የተማሩ ነበሩ። መንፈሳዊ ትምህርትን በሀገር ቤት፣ አለማዊ እውቀትን ደግሞ በውጭ ሀገራት የቀሰሙ ናቸው። ደርግ እነኝህን ረሽኖ ሀገሪቱን ለጋ ወታደሮች ተረከቡ። ይህም በተለይ በአማራ ላይ የትውልድ ክፍተትን ፈጠረ።
    ወያኔ በዘመኗ በአማራነታቸው ነጥላ 42 የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንን ከሀገር አባረረች። ይህ የምሁራንን ፍልሰት አባብሶ አስቀጠለው። ታግሎ ከማሸነፍ ይልቅ ተሰድዶ መገላገል አማራጭ ኃሳብ ሆኖ ቀጠለ። ይህም ሌላኛው የትውል ክፍተት የታየበት ክስተት ነው። በትሉ ውስጥ ዛሬ እየታዩ ላሉ ችግሮች ሁሉ የትውድ ክፍተቶቹ የተጫወቱት ሚና ጉልህ ነው።
    ዛሬም የአብይ አሕመድ አገዛዝ በተራው አማራን ከትምህርት በማግለል ሌላ የትውልድ ክፍተት እየፈጠረ ይገኛል። የአማራ ህዝብ ከ20 አመት በኋላ ምናልባት አንዳች ምሁር ላይኖረው ይችላል። ዳንኤል ክብረት “ወደ ድንጋይ ዘመን ትመለሳላችሁ” ሲል የነገረን ይህንን ነው።

    ታዲያ አማሮች ይሄን መቅዘፍት በትክክል ተረድተነው ይሆን? ከተረዳነው ትግሉ ለምን ይረዝማል?

  • የአፍህድ ሰብሳቢ አርበኛ አቶ እስክንድር ነጋ የደስታ መግለጫ ሰጡ!

    የጎንደርን አንድነት አስመልክቶ ከእስክንድር ነጋ (የአፋህድ ስብሳቢ) የተላለፈ የደስታ መልዕክት።
    /
    ጥቅምት 05፣ 2018 ዓ.ም።
    /
    ጤና ይስጥልኝ።

    የፋኖ አንድነት የአማራ ህዝብ የህልውና ትግልን ጥንካሬ፣ ተሰሚነት፣ ተዓማኒነት እና የመጨረሻ እጣ ፋንታ የሚወስን ወሳኝ ጉዳይ መሆኑ ለሁሉም ግልፅ የሆነ እውነታ ነው።

    የአማራ የህልውና ትግል ጠባብ የፖለቲካ ጥያቄዎችን ለማስፈፀም የሚደረግ ትግል አይደለም። ለአማራ ህዝብ የጄኖሳይድ የህልውና አደጋ ምንጭ ሆኖ የተገኘው ዘረኛው ህገ መንግሥት እንደ መሆኑ መጠን፣ ዓላማ እና ግቡ አሁን ያለውን ዘረኛ ሥርዓት ነቅሎ በአዲስ ህገ-መንግሥታዊ ሥርዓት መተካት ነው።

    ከዚህ አኳያ፣ ስለህገ -መንግስት ጉዳዮች ዓለም አቀፋዊ መርሆች እና መለኪያዎች ባሉበት ዘመን የምንኖር እንደ መሆናችን መጠን፣ ለፋኖ አንድነት መሠረት የሚሆኑት መርህዎች በአብዛኛው ተሠርተው ያለቁ ናቸው። እንደ አዲስ ተሠርተው ስምምነት የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች በቁጥር ትንሽ እና ቀላል የሆኑ ናቸው።

    ይህ መሠረታዊ እውነታ ጎልቶ በሚታይበት የትግል አውዳችን የፋኖ አንድነት እስካሁን እውን መሆን አለመቻሉ የፋኖ መሪዎችን በታሪክ ሲያስወቅስ የሚኖር ጥቁር ነጥብ ነው።

    “መልካም ነገር ከሚቀር፣ ረፍዶም ቢሆን መሆኑ ሰናይ ነው” እንደሚባለው ፣ አብዛኞቻችን የፋኖ መሪዎች በታሪክ ተጠያቂነት እንዳለብን ከተገነዘብን ውለን አደረናል። በሁሉም ወገን ይበል የሚያሠኙ ጅማሮዎችም አሉ።

    በዚህ መንፈስ፣ “እከሌ ነው ንፁህ፣ እከሌ ነው ጥፋተኛ” ሳይባባል፣ የአለፈውን ነገር ሁሉ ትተን ወደፊት ብቻ እየተመለከን ባለንበት ጊዜ፣ የአፋህድ እና የአፋብኃ አመራሮች በጎንደር ጠቅላይ ግዛት ጥቅምት 04፣ 2018 ዓ.ም ተገናኝተው፣ ከዚህ በኃላ በአንድነት ለመሥራት ሁላችንም ደስ የሚያሠኝ ተግባራዊ ሥራ ጀምረዋል ። መላው የአማራ እና የኢትዮጰያ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ።

    ግን ስራው ተጀመረ እንጂ አላለቀም። በጎንደር ያየነውን በአማራ ማሳደግ ይጠበቅብናል። በዚህ ረገድ የተጀመሩ የአንድነት ሥራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    ዘረኛው ሥርዓት በቀዳሚነት አማራን ለጅምላ ማንነት ተኮር ፍረጃ፣ ጥላቻ፣ መገለል፣ መፈናቀል እና ጭፍጨፋ ሰለባ ቢያደርግም፣ መርዝነቱ ግን ለመላ ኢትዮጰያዊያን ነው። ስለዚህም፣ በጎንደር የተጀመረው አንድነት፣ ወደ አማራ ካደገ ቦኋላ፣ መቋጫው በኢትዮጰያ ይሆናል።

    አመሰግናለሁ።

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!

    ክብር ለሰማዕታት!!!
    ዘላለማዊ ክብር ለፈጣሪ!!!

    እስክንድር ነጋ፣
    አፋህድ።

  • የሚሊሻ አባላት የሽዋ ፋኖን ተቀላቀሉ!

    የአፋህድ የጥቅምት 03 / 2018 ዓ.ም የአውደ ውጊያ ውሎ— በሸዋ በ100ዎች የሚቆጠሩ ሚሊሻዎች አፋህድን ተቀላቀሉ፣ የአገዛዙ 101ኛው ኮማንዶ የድረሱልኝ ጥሪ እያቀረበ ነው!!!
    //
    ጥቅምት 03 / 2018 ዓ. ም
    //
    በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በመርሀቤቴ ቀጠና ለበርካታ ቀናት ያለማቋረጥ እየተደረገ የሚገኘው ውጊያ እንደቀጠለ ሲሆን፣ የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አፄ አምደፂዮን ኮር አካል የሆነው ጀግናው አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ጥቅምት 02 / 2018 ዓ. ም በነበረው የውጊያ ውሎ፣ ከረፋዱ 5 ሰዓት አንስቶ የሬማ ከተማን ቀለበት ውስጥ በመስገባት የአገዛዙን ጦር መላወሻ አስጥቶት ውሏል።

    በሬማ ከተማ የሰፈረው የ101ኛው አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር እና በርካታ የክልሉ አድማ ብተና እና ሚሊሻ ኃይል ከጀግናው ሰራዊታችን የተከፈተበትን ጥቃት መቋቋም አቅቶት ባቀረበው አስቸኳይ የድረሱልኝ ጥሪ፣ ከዓለም ከተማ በ 2 ኦራል እና 2 አይሱዙ፣ እንዲሁም ከመራኛ ከተማ በ 3 ካሲዮኒ የተጫኑ እና እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ የመከላኪያ ወታደሮች ደርሰውለታል።

    ተጨማሪው አዲሱ ሠራዊት ወደ ከተማ እንዲገባ ሆን ብሎ ያሳለፈው ሠራዊታችን፣ በከተማዋ ዙሪያ ያለውን ከበባውን ይበልጥ አጠናክሮ የአገዛዙን ጦር ይበልጥ መፈናፈኛ አሳጥቶት ይገኛል። የአገዛዙን አጣቢቅኝ ውስጥ መግባት በአግባቡ የተረዱ በተለያየ ቦታ ላይ የሚገኙ ቀይ ቦኔት የሚያደርጉ የመከላኪያ ኮማንዶ አባላት፣ ከምድባቸው በሌሊት እየጠፉ በሁሉም ቦታ ባሉ ክፍለ ጦሮች እየተቀላቀሉ ይገኛሉ። የፎቶ ምስላቸውንም በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል።

    ሰሞኑን በተከታታይ በተደረጉ ውጊያዎች አገዛዙ ተስፋ እንደሌለው የተረዱ እና በጀግና ተዋጊዎቻችን ጀግንነት የተደመሙ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሚሊሻ አባላት፣ ከተጠረነፉበት ካምፕ በሌሊት ጠፍተው በቲም እና በጋንታ ሆነው በነጋታው ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ጀግናው ሠራዊታችንን በተለያዩ የሸዋ ቀጠናዎች ተቀላቅለዋል። የፎቶ ምስላቸው በከፊል ከዚህ መግለጫ ጋር አያይዘናል። በቀጣይ ቀናት በቪዲዮ መግለጫ ይሰጣሉ።

    ለሚሊሻ አባላቱ ሞቅ ያለ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን፣ የተሃድሶ ትምህርት ተሰጥቷቸው የህልውና ትግሉን በሚመቻቸው እና በሚፈቅዱት አግባብ የሚያግዙበት ሁኔታ ይመቻችላቸዋል።

    በቀጠናው ሠራዊታችንን በፈቃዱ የሚቀላቀለው የሚሊሻ አባላት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህን የተረዳው አገዛዙ የሚሊሻ ኃይሉ እንዳይናድበት የተለያዩ ህገ ወጥ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል። የሰብአዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅቶች ይህን ጉዳይ በአንክሮ እንዲከታተሉት በዚህ አጋጣሚ ጥሪ እናቀርባለን።

    በሌላ ግንባር፣ በሞረት እና ጅሩ ወረዳ፣ በሲያዳብርና ዋዩ፣ በእንሳሮ እና ለሚ እስከ ደብረሊባኖስ ገዳም ድረስ ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሰው የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ የአፄ አምደፂዮን ኮር አካል የሆነው ጀግናው የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር በአካባቢው ካሉ የአባት አርበኞች ጋር ተጣምሮ በብቃት እየተፈፀሙ በሚገኙ የተጠኑ ኦፐሬሽኖች በአገዛዙ ጦር ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሱበት ይገኛሉ።

    በዚህም የተደናገጠው የ101ኛው ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃ ከአንዱ ሻምበል ላይ ስድስት አባላቶቹ ብቻ ሲቀሩ እና አብዛኛው ወደየመጣበት ሲበተን፣ ሦስት አባላቶቹ ደግሞ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ጀግናው ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል። የፎቶ ምስላቸውን ከዚህ መግለጫ ጋር አያይዘናል።

    ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
    //
    ጥቅምት 03 / 2018 ዓ.ም

  • በሽዋ እና በጎንደር አፋህድ ከፍተኛ ድል አስመዘገበ

    የአፋህድ የጥቅምት 01፣ 2018 ዓ.ም የአውደ ውጊያ ውሎ–በሸዋ እና ጎንደር የአገዛዙ ጦር ከፍተኛ ሽንፈት ደረሰበት!!!
    //
    ጥቅምት 01፣ 2018 ዓ.ም
    //
    የአፋህድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የመሐመድ ቢሆነኝ ኮር አካል የሆነው ጀግናው ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር ፣ ጥቅምት 01፣ 2018 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ፣ አፄ ዘርያቆብ ክፍለ ከተማ፣ 06 ቀበሌ በሚገኘው እና የአገዛዙ መከላከያ ጦር፣ የክልሉ አድማ ብተና እና የሚሊሻ ኃይል በጥምረት እንደ ዋና ማዘዣ ጣቢያ በሚጠቀሙበት የጦር ካምፕ ላይ ከሌሊቱ 10:30 በፈፀሙበት መብረቃዊ ጥቃት ከፍተኛ ድል ተቀዳጅተዋል።

    በሁለት አቅጣጫ ሰርገው የገቡት ጀግና ተዋጊዎቻችን፣ ከሌሊቱ አስር ሰአት ተኩል ጀምረው እስከ ጠዋቱ አንድ ሰዓት ድረስ ባደረጉት ውጊያ፣ በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሰውበታል። በጀግኖቻችን ድንገተኛ ጥቃት የተደናበረው የአገዛዙ ጥምር የጦር ኃይል፣ በደብረ ብርሃን ዙሪያ ያሉትን ኃይሎች አሰባስቦ የመልሶ ማጥቃት ሙከራ ቢያደርግም ሳይሳካለት ቀርቷል። በአገዛዙ ዋነኛ ማዘዣ ላይ የተፈፀመው ይህ ድፍረት የተሞላበት ጥቃት፣ የአገዛዙ ቁመና ሙሉ ለሙሉ ወደ መከላከልነት እንደወረደ እና ፋኖ ወደ አጥቂነት እየተሸጋገረ መሆኑን በገሃድ ያሳየ ነው። የአውደ ውጊያው ሙሉ መረጃ በቀጣይ ቀናት ይፋ ይሆናል።

    የአፋሕድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው ጀግናው አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ፣ በዛሬዋ ዕለት፣ ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ከጠዋቱ 2 ሰዓት አንስቶ፣ ከወሎ ጠቅላይ ግዛት በቅርብ እርቀት በምትገኘው ሬማ ከተማ ዙሪያ አገዛዙ በከንቱ በልዩ ሁኔታ ከሚተማመንባቸው የጦር ምድቦቹ አንዱ ከሆነው 101ኛው አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ጋር በሁለት አቅጣጫዎች እልህ አስጨራሽ ውጊያዎች አድርጎ ከባድ ጉዳት አድርሰውበታል።

    ከሬማ ከተማ በስተ ምዕራብ በኩል በሚገኙት በቢራባ ቀበሌ፣ በመጅት ቀበሌ፣እንዲሁም ፍልሚያው አድማሱን ካሰፋ በኋላ እስከ አላቦ ቢራባ ቀበሌ ድረስ በሸፈነው የውጊያ ቀጠና፣ አገዛዙ ሙሉ ኃይሉን እንዲሳተፍ ከማድረጉም ባሻገር፣ ከወትሮው በተለየ መልኩ የክፍለ ጦሩ አመራሮች ውጊያውን በቅርብ ክትትል እንዲመሩት ቢደረግም፣ ጀግኖቻችን በጨበጣ ውጊያ ተናንቀውት ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበታል።

    በሌላኛው አቅጣጫ፣ ከሬማ ከተማ በስተሰሜን በኩል በአዝማ ቀበሌ፣ በዩጎብያ ቀበሌ፣ እንዲሁም፣ ፍልሚያው ሲጋጋል የሸፈሬ አንባ ቀበሌዎችን አካቶ ሰፋ ባለው የአውደ ውጊያ ቀጠና ጠላት ምንም የተለየ ነገር ማምጣት ባለመቻሉ የወታደራዊ ቁመናው ጀርባ አከርካሪው ላይ ተመቷል።

    በሬማ ከተማ መሽጎ ሽንፈት ሲያስተናግድ የዋለው የአገዛዙ ጦር፣ ከመርሀቤቴ ወረዳ አለም ከተማ እና ከሚዳ ወረዳ መራኛ ከተማ ተጨማሪ ኃይል ጠይቆ የደረሰለት ቢሆንም፣ በዕለቱ የውጊያ ውጤት ላይ ምንም ያመጣው ለውጥ የለም።

    በዛሬው አውደ ውጊያ በቀጠናው ያሉ የአርበኞች ፋኖ ጉልህ ድርሻ የነበራቸው ሲሆን፣ ህዝባዊ አደረጃጀቶቻችን ከፍተኛ የእድገት ደረጃ እና ብስለት እያገኙ ለመሆናቸው ተጨባጭ ማሳያ ነው። በነፃ ወረዳዎቻችን የብልፅግና ዘረኛ የኃይል አገዛዝ ከስር መሠረቱ ተነቅሎ ተጥሏል።

    በዕለቱ በነበረው ውጊያ ለግዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ የጠላት ኃይል ተደምስሷል፣ ምርኮኞችም የተያዙ ሲሆን፣ የዓለም አቀፍ ህግን በጠበቀ መልክ ወደማቆያ ስፍራ ተወስደዋል።

    በሌላ በኩል፣ የአፋሕድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው ጀግናው ራንቦ ክፍለጦር፣ በይፋት አውራጃ አርማኒያ ከተማ፣ ልዩ ስሙ “አስፍቸው” በተባለ ቦታ ዛሬ ጥቅምት 01፣ 2018 ዓ.ም በፈፀመው ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት፣ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሷል።

    መነሻውን ከደብረ ብርሃን ከተማ አድርጎ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የተለያዩ አካባቢዎች መሽገው መንቀሳቀሻ ላጡ የአገዛዙ የጦር ሬሽን ላማድረስ የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ጦር ላይ በተወሰደው በዚህ የደፈጣ እርምጃ፣ በወገን በኩል ከታሰበው በላይ ውጤት ተመዝግቦበታል።

    የአፋህድ የጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ
    206ኛ ኮር በሚንቀሳቀስበት በስማዳ ወረዳ ደግሞ፣ መስከረም 30፣ 2018 ዓ.ም የፋኖ ኃይልን በከበባ እደመስሳለሁ ብሎ ወደ “የኳሳ” አካባቢ የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል፣ በጀግናው ጄኔራል ኃይሌ-ዘ-ውባንተ ክፍለ ጦር ተወርዋሪ ኃይል መንገድ ላይ ቀለበት ውስጥ እንዲገባ ተደርጎ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል።

    ሁለት ዲሽቃዎች፣ ስድስት ብሬኖች እና ዘጠኝ ስናይፐሮች ይዞ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል፣ በሸረፍጎዲ እና በኮሽ አካባቢ ሲደርስ ደግሞ፣ አድፍጦ በጉግት የጠበቀው ጀግናው የጉና ክፍለ ጦር ከፍተኛ ጉዳት አድርሶበታል።

    በጥቅሉ መስከረም 30፣ 2018 ዓ.ም የአገዛዙ ጦር ሙት እና ቁስለኛ ከመሆኑም ባሻገር፣ በርካታ መሣሪያዎችም በምርኮ ተይዘዋል። በጠላት ላይ የደረሰው ጉዳት ይህ መግለጫ እስከሚወጣበት ግዜ ድረስ እየተጣራ ይገኛል፣ በሂደት ይፋ ይሆናል።

    ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!!!

    ድል ለአፋህድ እና የአማራ ፋኖ ሁሉ!!!
    ድል ለአማራ ህዝብ!!!
    ድል ለኢትዮጰያ ህዝብ!!!
    //
    ጥቅምት 01፣ 2018 ዓ.ም

  • ለ2 የተከፍሉትን ፋኖዎች እንድ እንዲሆኑ ስንለምን 3ኛ ቡድን ለምን አስፈለገ?

    3ኛ የፋኖ ቡድን ለምን አስፈለገ?
    …………………………………….
    ከሞገድ እጅጉ

    ጊዜ የሚሰጥ ሁኔታ ላይ አይደለም ያለው የአማራ ህዝብ። በሁለንተናዊ መልኩ መቶ አመት ወደኋላ መልስናቸዋል ያለው አንድ ወቅት የአብይ አህመድ mouthpiece ይሆነው ሽመልስ አብዲሳ እውነቱን ነው።አሁን የቀራቸው አማራን መቶ በመቶ ማጥፋት ነው።ለመሆኑ ወንጌላዊው ብልጽግና የኦሮሙማ አፓርታይድ የፈለገውን እንዲያደርግ የፈቀድለት፡ ብሎም የተባበርነው እኛ አማሮች መሆናችን ስንቶችቻችን ገብቶን ይሆን? .,…..

    የአማራን ህዝብ ስቃይ የሚታደርገው ግን የለም፡፡ ይሄ ሁሉ የአማራና ምሁር እና ፖለቲከኛ ሀቁን ቢያውቀውም ተግባራዊ ማድረግ ግን አልቻለም፡፡
    ሀቁን እንቀበል ከተባለ፤ በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ይሄ ሁሉ ስቃይና መከራ በአብይ አህመድ ጥንካሬ አይደለም፤ ይልቁንም በአማራ ምሁራን እና ፖለቲከኞች ደካማነት ነው፡፡ የአብይ አህመድ ጭካኔ፣ ኢሰብዓዊነትና አረመኔነት ተፈጻሚ የሆነው በብአዴን አስፈፃሚነት እና ተቃዋሚ ነን በሚሉ የአማራ ኃይሎች በፍጥነት አለመደራጀት ነው፡፡ከተደራጁም እርስበርስ መጠላለፍ የተቃዋሚ አማራዎች የባህሪ መገለጫ እስከመሆን ደርሷል።
    ከዚህ በኋላ ብአዴንንም ሆነ ኦህዴድን መውቀስ ጅልነት ነው፡፡ ኦህዴድ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን ዕቅዱን እያሳካ ነው፡፡ ብአዴንም ተላላኪነትና ሆዳምነት ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የኖረበት መሰረታዊ ባህሪው ሆኗል፡፡ አሁን ችግሩ ያለው በተቃዋሚ የአማራ ፖለቲከኞች ዘንድ ነው፡፡
    እየሆነ ያለው ነገር ፋታ የሚሰጥ አይደለም፡፡ አብይ የአማራ ሕዝብ ችግርንና ስቃይን እንድላመድ ተደርጓል፡፡ የአማራ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የአዲስ አበባም ሆነ ሌላው ለጊዜው ጦርነት የሌለበት አካባቢ ያለው ሕዝብ ችግርን እንድላመድ ተደርጓል፡፡ ለምን የሚለውን ልብ ብለን እንመልከት፡፡ ይህን ሀቅ አለመቀበል ደግሞ ዋጋ ያስከፍላል፡፡
    በአማራ ሕዝብ ላይ የተቃጣውን የኦህዴድ ወረራ ለመመከት የፋኖ እንቅስቃሴ ሲጀመር በአዲስ አበባ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ነበር፡፡ እንደ ታላቁ ሩጫ ባሉ ሕዝባዊ ትዕይንቶች ላይ ‹‹እየመጡ ነው…›› በሚል ለፋኖ ድጋፍ ይደረግ ነበር፡፡ አማራ ክልል ውስጥ የሚፈፀም ጥቃት በማህበራዊ ገጾች መነጋገሪያ ይሆን ነበር፡፡
    አሁንስ?
    አሁን ተለምዷል፡፡ ሁሉም እየኖረ ያለው የዕለት የዕለቱን ነው፡፡ ሁሉም እየኖረ ያልው የፊት የፍቱን ነው። በድሮን ብዙ ሕዝብ ተጨፍጭፎ ምንም ስሜት የማይሰጥበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በአማራ ክልል ውስጥ ካህን በመቅደስ ውስጥ ተገደለ ማንም ደንታ የለውም። የዛሬ አመት ገደማ በምዕራብ አርሲ አንድ ካህን ከነ ከ13 ቤተሰባቸው በጥቅሉ 34 አማሮች ታረዱ በዛው እለት በቀለም ወለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተጨፍጭፈው አድረው
    የአማራ ልጆች ግን ፤ብዙዎች ግን “ኢኳቶሪያል ጊኒ ውስጥ ከትዳሩ ውጭ የወሰለተ ሰው” ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ነበር።
    የዛሬ 5 ሳምንት በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ንጹሀን አማሮች ሲጨፈጨፉ አደሩ ማንም ቦታ የሰጠው የለም። ።አብዛኛው የአማራ ማህበራዊ ሚዲያ አክቲቪት ነን ባይ “”የሚወሩት ስንፈተ ወሲብን እንዲት መከለከል ይቻለል የሚል ሆነ”
    ሰዎች ትልልቅ ነገሮችን ትተው ትንንሽ ነገሮች ላይ ብቻ እያተኮሩ የዕለት የዕለቱን ብቻ እንዲኖሩ አድርጓል፡፡
    ይህ አጋጣሚ የተፈጠረበት ምክንያት በተቃዋሚ ፖለቲከኞች ላይ ያለው ተስፋ ስለተቀዛቀዘ ነው፡፡ ከአገዛዙ የተሻለ አርቆ አስተዋይነት የሌላቸው ሆነዋል ብሎ ተስፋ ከመቁረጥ ነው፡፡
    ደፈር ብለን እውነቱን እንናገር ከተባለ፤ የፋኖ ትግል በፍጥነት ወደ ውጤት እንዳይመጣ ያደረገው ፖለቲከኛውና የአማራ ምሁር የሚባለው ነው፡፡ ልብ መባል ያለበት ነገር በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ጥይት በመተኮስ ብቻ መንበረ መንግሥትን መቆጣጠር አይቻልም፡፡ የኮምኒኬሽን ትግል ያስፈልጋል፡፡ የአማራ ምሁራን እና ፖለቲከኞች የኮምኒኬሽን ትግል ደግሞ ደካማ ነው ብቻ ሳይሆን የሞተ ነው ማለት ይቻላል፡፡ አርቆ አስተዋይነትና ብልህነት የለውም፡፡ ዕለታዊ ስሜት የተጫነው ነው፡፡
    ወዲህ ደግሞ እጅግ አደገኛ የሆነ ጎጠኝነት አለበት፡፡ አገዛዙን ከመታገል በላይ እርስ በእርሳቸው የሚታገሉት ይበልጣል፡፡ ይህ ደግሞ የሚጠቅመው አገዛዙን ነው፡፡ ይህን እንኳን አርቆ አለማስተዋል የአማራ ሕዝብ ጠላትነት ነው፡፡
    ወቅታዊ ብሽሽቅ እና እልህ ከጀግና አይጠበቅም፡፡ ጀግና ማለት የራሱን የግል ክብር ሳይሆን የሕዝቡን ክብር የሚያስቀድም ሲሆን ነው፡፡ አንድ ሰው ጀግና ነኝ ካለ፤ ራሱ ተዋርዶም ቢሆን የሕዝቡን ዘላቂ ክብር ያስጠብቃል፡፡
    መሬት ላይ የሚታየው ነገር ግን ‹‹እኔ ተናግሬ ነበር›› ለማለት እንዲያመቻቸው እነርሱ ያሉት እንዲሆን የትኛውንም ነገር የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እኔጋር ያለ ነገር ብቻ ነው መፍትሄው አይነት የእነርሱ ትንቢት ይሰምር ዘንድ ሕዝብን አደጋ ላይ የሚጥል ነገር የሚያደርጉ ከችግሮቹ ውስጥ ጎልቶ የሚታዩት ናቸው፡፡

    ስንት የቤት ስራ እያለ ፦

    የአማራ ሕዝብ በየዕለቱ እየተጨፈጨፈ፤ የማይመለከታቸውን የግለሰብ ጉዳይ ያነሳሉ፡፡ የዘር ጭፍጨፋውን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ማሳወቅና ለሚጨፈጨፈው ሕዝብ ድምጽ መሆን ሲገባቸው፤ ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር የማይገናኝ ያረጀ ያፈጀ የግለሰብ ጉዳይ አንስተው ይጨቃጨቃሉ፡፡
    ታዲያ እነዚህ ምሁራን እና ፖለቲከኞች ከገዳዩ የአብይ አህመድ አገዛዝ በምን ይለያሉ? በአንድ ፊቱኑ የተለየለት ጠላት አይሻልም ወይ?

    እነዚህ በራስ ፍቅር የወደቁ ው እና አርቆ ማሰብ የተሳናቸው የአማራ ፖለቲከኞችና ምሁራን የአብይ አህመድ አገዛዝ ዕድሜ እንድኖረው አድርገዋል፡፡
    እሳት የሚተፋውን የፋኖ ትግል ውሃ ቸልሰውበታል፡፡ በቀን በሺዎች የሚቆጠር ወታደር የሚመረክበትን የአብይ አህመድ አገዛዝ ዕድል ሰጥተውታል፡፡ የአብይ አህመድ አገዛዝ ይህን ያህል የተዳከመው በፋኖ የመሬት ላይ የትጥቅ ውጊያ ብቻ ነው፡፡
    በፕሮፖጋንዳ አንዲት ፐርሰንት አልታገዘም ማለት ይችላል፤ እንዲያውም መሰናክል ነው የሆኑበት፤ ቢያንስ ቢያንስ አርፈው ቢቀመጡ ይሻል ነበር፡፡
    የአብይ አህመድ አገዛዝ ወታደር አልቆበታል፡፡ የአገሪቱን ድንበር ባዶ አድርጎ ወደ አማራ ክልል ያሰማራው ሠራዊት ሁሉ ተማርኮበት አሁን ከየመስሪያ ቤቱ በግዳጅ መመልመል ጀምሯል፡፡ በቅርቡ በወጣ ዘገባ እንዳየነው፤ ከአዳማና አዲስ አበባ ወጣቶች በብዛት እየታፈሱ ነው፡፡

    አብይ አህመድን ለዚህ ሁሉ መዳከም ያበቃው የፋኖ የትጥቅ ትግል ብቻውን ነው፡፡ በሰለጠነ ኮምኒኬሽን እና ፕሮፖጋንዳ ቢታገዝ ኖሮ ይህን ጊዜ የአማራም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብይ አህመድን ተገላግሎት ነበር!
    አሁን በዚህ ሳምንት እንኳ ሁለት የካቢኔ ሚንስትሮች ከስራ ተብረዋል ለገሰ ቱሉ እና ማሞ ምርቱ ይህ የሚያሳየው የመንግስትን ድክመት እንጂ ጥንካሬ አይደለም።
    እናም
    መደምደሚያ፦
    “ይህ እርስ በእርሱ የሚጠላለፍ የአማራ ምሁርና ፖለቲከኛ ሁሉ የአብይ አህመድ አገዛዝ እንዲቀጥል የሚያደርግ የአማራ ሕዝብ ጠላት ነውና አንድ ሊባል ይገባል!”
    *** በመላ አውሮፓ 72 የአማራ ፓርቲዎች አሉ***ምን ፈየዱ ነገር አለ ቢባል “ዜሮ” ነው መልሱ።ፋኖን ም እንደ ቅንጅት?*** እንጠይቃለን?

    እንመልሳለን ***በቃ***